Jump to Navigation

New Construction Industry Policy Drawn Up

Published on: Sun, 2013-11-03 00:00
image of construction workers

የግንባታ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚገጥሙትን ውስብስብ ችግሮች መፍታት የሚረዳ አዲስ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ ተረቀቀ።

የከተማ ልማት ፣ የኮንስትራክሽንና ቤቶች ግንባታ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ኃይለሚካኤል ተፈራ እንደተናገሩት ፥ መንግሥት የዘርፉን ተግዳሮቶች ለማስወገድ የተለያዩ እርምጃዎች ሲወስድ ቆይቷል።

በኢንዱስትሪው ከሚታዩት ችግሮች መካከል ዋነኛው የግንባታ ፕሮጀክቶችን በታለመለት ጊዜና ወጪ በአግባቡ አለመፈጸም አንዱ መሆኑን ጠቁመው ፥ የግንባታው ዘርፍ ሥርዓት ባለው መንገድ እንዲመራ አዲስ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ መዘጋጀቱን አመልክተዋል።

ፖሊሲው የግንባታው ኢንዱስትሪ ተስማሚ ቴክኖሎጂ እንዲጠቀምና የአገሪቱን የግንባታ ዘርፍ አቅም እንዲገነባ የሚያደርግ ከመሆኑ ባሻገር የፈጠራ ሥራን የሚያበረታታ ፣ ስነ-ምግባራዊ የሥራ አፈፃጸም እንዲሰፍን የሚያደርግ መሆኑን አብራረተዋል።

በተጨማሪም ፖሊሲው የሥራ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሥርዓት እንዲኖር ከማስቻሉም በላይ ኢንዱስትሪው የግንባታ ሕግና ሥርዓት ተከትሎ እንዲጓዝ የሚያስችል መሆኑን የዘገበው ኢዜአ ነው።
Source: Fana Broadcasting Corporate (FBC)



Main menu 2

Lambadi Software Developer P.L.C